የዋና ስራ አስፈፃሚዉ መልእክት
የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የአገልግለት ዕለትን ለተገልጋይ ብቻ በማዋል የህዝብ እሮሮን ለመቀነስ ብሎም በተገልጋዮች የሚነሱ አንገብጋቢ የሆኑ ጥያቄዎችን በአግባቡ አድምጦ ለመመለስ በሁሉም ጽህፈት ቤቶች አገልግሎትን በአንድ ማዕከል መስጠት ከጀመረ ጊዜያትን አስቆጥሯል ፡፡
በተለይም በተለያዩ ምክንያቶች ለአሳዛኝ ችግሮች የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን በርህራሄ እና በአክብሮት እያዳመጠ ህግና መመሪያ በሚፈቅደው መንገድ ለሚነሱት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠትና በመፍታት፤ችግሮችና ቅሬታዎች ወደተነሱበት ተቋማት በቀጥታ ስልክ በመደወልም ጭምር በግልፅ በማነጋገር እልባት እየሰጠ ይገኛል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላልና ተገልጋዮቻችን ወደ እኛ ኑ ጥያቄያችሁን አቅርቡ። በእኛ ደረጃ የምንፈታውን ፈጣን ምላሽ እንሰጣለን ። ከኛ በላይ የሆነውን ለሚመለከተው አካል እናስተላልፋለን። የማንፈታውን ከእናንተ ጋር እንግባባለን። ይህ የ2018 የአገልግሎት አሰጣጥ መርሀችን ነው። .... ተጨማሪ ያንብቡ
አቶ ደረጄ ፈይሳ , የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ






















