image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ለስራ ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች የልል ክህሎት ስልጠና ተሰጠ።

መስከረም 27, 2017
በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ ኢ/ር ይትባረክ ብርሃነ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት በስራ ላይ ማድረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይ እና ስራቸውን በእውቀት እንዲሰሩ ማድረግ ውጤታማነታቸው ላይ ያለው አስተዋፆ ከፍተኛ በመሆኑ ስልጠናውን በአግባቡ መከታተል ይገባቸዋል ብለዋል ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚረዳም ገልጸዋል። የወረዳው ም/ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ የክቴ የማታው ስልጠናው ለስራ ውጤታማነት አቅም የሚፈጥርና የሚያግዝ መሆኑና እንዲሁም በሚመርጡት የስራ ዘርፍ ስራውን በእውቀት እንዲሰሩ ከማገዝ አኳያ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውና በቀጣይም ስልጠናውን ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው በአፅንኦት ገልፀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች